Saturday, September 14, 2013

የዘመን አቆጣጠር ባሕረ ሐሳብ -ክፍል 5 -አበቅቴ እና መጥቅዕ

አበቅቴ እና መጥቅዕ
አበቅቴ የሚለው ቃል አፖክቴ ከሚለው የግሪክ ቃል የተገኘ ሲሆን ተረፈ ዘመን፣ ስፍረ ሌሊት ቁጥረ ሌሊት ማለት ነው። ተረፈ ዘመን የተባለበት ምክንያት ፀሐይና ጨረቃ በአንድ መስኮት ውስጥ የተፈጠሩ ሲሆን ዑደት በሚያደርጉ ጊዜ ግን በተለያየ ቀን ዑደታቸውን ይፈጽማሉ። በዚህም የተነሳ በመካከላቸው የቀናት ልዩነት የሚኖር ሲሆን ይህ ልዩነት አበቅቴ ወይም ተረፈ ዘመን ይባላል።
 የፀሐይ አንድ ዑደት 365 ቀን ከአስራ አምስት ኬክሮስ /ከስድስት ሰዓት/ ሲሆን የጨረቃ አንድ ዑደት ደግሞ 354 ቀን ከሃያ ሁለት ኬክሮስ ነው። ስለዚህ የጨረቃ ዑደት ፀሐይ ላይ ለመድረስ አስራ አንድ ቀን ይቀራታል። ይህ ቀሪ /አስራ አንድ/ አበቅቴ  እንግዲህ ጥንተ አበቅቴ አስራ አንድ ቢሆንም ይህ ቁጥር በየዓመቱ አስራ አንድ ቀን ስለሚጨምር ማለትም የጸሐይና የጨረቃ ዑደት በመጀመሪያው ዓመት አስራ አንድ ቢሆንም በሁለተኛው ዓመት የራሱ አስራ አንድና ያለፈው ዓመት አስራ አንድ ሲደመር ሃያ ሁለት ይሆናል። የሶስተኛው ዓመት አስራ አንድ ሲጨመር ሰላሳ ሶስት ይሆናል። ማንኛውም ቁጥር ከሠላሳ ከበለጠ በሠላሳ ይገደፋል ፡፡ስለዚህ ሠላሳ ሶስት በሠላሳ ሲገደፍ ወይም ለሠላሳ ሲካፈል አንድ ጊዜ ደርሶ ሶስት ይቀራል። ሶስት አበቅቴ ሆነ ማለት ነው። እንደዚህ በየዓመቱ አስራ አንድ እየጨመርን አበቅቴን ማግኘት ይቻላል። ነገር ግን የብዙ ዓመታት በሆኑ ቁጥር በዚህ መልኩ ማውጣቱ ስለሚከብድ በቀላሉ የየዘመኑን ወይም እኛ የምንፈልገውን ዓመተ ምህረት አበቅቴ ማውጣት እንችላለን። ይህንንም በሶስት ዓይነት መንገድ ማውጣት ይቻላል።   
1ኛ. አበቅቴን በወንበር ማውጣት
ከዚህ ቀደም ስለ ወንበር ስንመለከት ወንበር የሚጠቅመው የየዘመኑን አበቅቴና መጥቅዕ ለማግኘት ነው ብለናል። ስለዚህ ወንበርን በጥንተ አበቅቴ አባዝተን የምናገኘውን ቁጥር በሠላሳ ገድፈን ወይንም ለሠላሳ አካፍለን የምናገኘው አበቅቴ ይሆናል። 

Wednesday, September 11, 2013

የዘመን አቆጣጠር ባሕረ ሐሳብ -ክፍል 4 -ወንበር

ወንበር
በዓላትንና አጽዋማትን ለማውጣት ከሚያስፈልጉን ነገሮች ውስጥ አንዱ መጥቅዕ ሲሆን በዓላትና አጽዋማት የሚያድሩባቸውን ሌሊት የሚያሳውቀን ደግሞ አበቅቴ ነው። አበቅቴና መጥቅዕ በየዘመኑ የሚቀያየሩ ስለሆነ ሁልጊዜ ማለትም በየዓመቱ የየዘመኑን አበቅቴና መጥቅዕ ማውጣት ይኖርብናል። እንግዲህ ወንበር እነዚህን አበቅቴንና መጥቅዕን የምናወጣበት ቁጥር ነው። ወንበር የሚለው ስያሜ የተገኘው አበቅቴም ሆነ መጥቅዕ /ለበዓላትና ለአጽዋማት መገኘት ወሳኙ የሆኑ ነገሮች/ የሚገኝበት ከመሆኑም በላይ ዓመቱን ሙሉ ቀሚ በመሆን የሚያገለግል ቁጥር ስለሆነ ነው።
ንበር እንዴት ይወጣል?
ወንበርን በተለያየ መንገድ ማውጣት የምንችል ሲሆን ሊቃውንት አባቶቻችን እንደ ዛሬው የሂሳብ መቀመሪያ መሳሪያዎች ሳይኖሩ የሂሳብ ስሌቶችን የሚሰሩት በቃላቸው ነበር። አሁንም አብዛኛዎቹ በቃላቸው ነው የሚሰሩት። ለምሳሌ አንድን ትልቅ ቁጥር ለሆነ ቁጥር ማካፈል ቢፈልጉ /ለምሳሌ 7450ን ለ532 ለማካፈል/ የሚጠቀሙት እንደኛ ካልኩሌተር ሳይሆን በቃላቸው ነው የሚያካፍሉት። በዚህን ጊዜ ይንን ትልቅ ቁጥር ለማካፈል የተለያዩ መንገዶችነ ይጠቀማሉ። ስለዚህ ይህንን የአባቶችን ትውፊት መተው ተገቢ ስላልሆነ እንዲሁም አንዱም መንገድ በመሆኑ እንመለከተዋለን። ሌላው ደግሞ ዘመኑ የሰጠንን አጭር መንገዶችንም መጠቀሙ ለስራችን ቅልጥፍና የሚሰጠው በመሆኑ በዘመናዊ መንገድ በማለት እንመለከተዋለን።

Tuesday, September 10, 2013

የዘመን አቆጣጠር ባሕረ ሐሳብ -ክፍል 3 - ሰባቱ አዕዋዳት

አዕዋዳት
አዕዋዳት የሚለው ዖደ ከሚለው ግስ የተገኘ ሲሆን ዞረ ማለት ነው። አዕዋዳት ደግሞ በብዙ እየዞረ የሚመጣ ማለት ነው። የኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ጥንት ይጀምራል። ጥንትነቱም ከፍጥረተ ዓለም፣ ከፍጥረተ ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብት ነው። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ሳድሲቱ ዐምሲት፣ ዐምሲቱ ራብዒት፣ ራብዒቱ ሳልሲት፣ ሳልሲቲ ካልዒት፣ ካልዒቱ ኬክሮስ፣ ኬክሮሱ ሰዓታት፣ ሰዓታቱ ሳምንታት፣ ሳምንታቱ  ወራት፣ ወራቱ ዓመታት፣ ዓመታቱ አዝማናት እየሆኑ ዛሬ ካለንበት ላይ ደርሰል።
ሳድሲት፣ ሃምሲት፣ ራብኢት … ወዘተ ተብለው የተገለጹት በዘመናዊው አነጋገር ማይክሮ ሰከንድ፣ ሚሊ ሰከንስ፣ ሰከንድ … ወዘተ እንንደሚባሉት እጅግ በጣም ደቃቅ የሆኑ የጊዜ መለኪያዎች ናቸው። ጊዜያቸው ወይም ቆይታቸው ከዓይን ቅጽበት ያነሰ በመሆኑ አንጠቀምባቸውም፤ በዚህም ምክንያት የተለመዱ አይደሉም። ዓለምከተፈጠረ ዘመን ከተቆጠረ በፀሐይ 5005 ዓመተ ዓለም ነው። ይኸውም 
. ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት የነበረው 5500 ዘመን ዓመተ ፍዳ ዓመተ ኩነኔ ይባላል።በሐሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ - አምስት ቀን ተኩል ሲፈጸም ከልጅህ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው” /ቀሌምንጦስ/ እንዳለው አምስት ቀን ተኩል የተባለው ይህ አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ማለት ነው። ይህ ሲተነተን  
             ከአዳም እስከ ኖህ ያለው ዘመን 2250                                                   
             ከኖህ እስከ ሙሴ               1588
             ከሙሴ እስከ ሰሎሞን           599
             ከሰሎሞን እስከ ልደተ ክርስቶስ 1063 ድምር 5500 ይሆናል።

Sunday, September 8, 2013

የዘመን አቆጣጠር ባሕረ ሐሳብ -ክፍል 2 -ቅዱስ ድሜጥሮስ

እንኳን ለዘመነ ማርቆስ 2006 ዓ.ም. በሰላም አደረሳችሁ  
ዕንቁጣጣሽ
አዲሱ ዓመት የንስሐ ፤ የቅድስና ፤ የደስታ ፤ የፍስ ፤ የፍቅር ያድርግልን

ቅዱስ ድሜጥሮስ ተካሌ ወይን

ድሜጥሮስ መስታወት ነው-በመስታወት ከዓይን ጉድፍ ከጥርስ እድፍ አይተው እንደሚያጸዱበት ሁሉ ባሕረ ሐሳብንም የተማረ ሰው ዓለም ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ እስከ ምጽአት ድረስ የሚሆነውን ቁጥር ያውቃልና፡፡ ባሕረ ሐሳብ ማለት ቁጥር ያለው ዘመን ማለት ነው፡፡ አንድም ሐሳብ ባሕር ይለዋል ዘመን ያለው ቁጥር ሲል ነው፡፡

ድሜጥሮስ መነጽር ነው፡- መነጽር የራቀውን አቅርቦ፣ የረቀቀውን አጉልቶ፣ የተበተነውን ሰብስቦ እንዲያሳይ እርሱም የተበተኑ አጽዋማትን በዓላትን አቅርቦ ያሳያልና፡፡
ድሜጥሮስ ጎዳና ነው፡- በጎዳናው ተጉዘው ከቤት እንደሚደርሱ ሁሉ፣ ባሕረ ሓሳብም ወደ ኋላ ያለፉትን ወደፊትም የሚመጡትን አጽዋማት በዓላትን ለይቶ ያሳውቃልና፡፡
 ድሜጥሮስ ተራራ ነው፡- በተራራው ጫፍ ላይ በወጡ ጊዜ ምንጩ ሜዳው፣ ግጫው፣ ኮረብታው እንደሚታይ ሁሉ ድሜጥሮስም የአጽዋማት በዓላትን ኢየዓርግ ኢይወርድ ጠንቅቶ ጽፏልና፡፡
ድሜጥሮስ መስተገብረ ምድር (በግብርና የሚተዳደር) ነው፡- 
ይህስ ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ፡-