Friday, June 24, 2011

ቅዱሳን ሐዋርያት ክፍል ፪

የሐዋርያት ዝርዝር
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሐዋርያት ዝርዝር በአራት ቦታዎች ተጽፎ ይገኛል፡፡ እነዚህ ዝርዝሮች በማቴዎስ፣ በማርቆስና በሉቃስ ወንጌሎች ሲገኙ በዮሐንስ ወንጌል ግን ዝርዝሩ አልሠፈረም፡፡ የመጨረሻው ዝርዝር የሚገኘው በሐዋርያት ሥራ ላይ ነው፡፡
ሐዋርያት  በበዓለ ሃምሳ

Wednesday, June 22, 2011

ቅዱሳን ሐዋርያት ክፍል ፩

መግቢያ
መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በ30 ዘመኑ በማየ ዮርዳኖስ በዕደ ዮሐንስ ተጠምቆ 40 ቀንና ሌሊት በገዳመ ቆሮንቶስ ከጾመ ከጸለየ በኋላ የማስተማር ሥራውን ሲጀምር አስቀድሞ ያደረገው ነገር ቢኖር ቃሉን ተምረው ሰምተው ተአምራቱን አይተው ዳስሰው በዓለም ዞረው ወንጌልን የሚሰብኩ ደቀ መዛሙርቱን መምረጥ ነበር፡፡ እነዚህ ደቀ መዛሙርቱም ሐዋርያት ተብለው ይጠራሉ፡፡



ሐዋርያ የሚለው ቃል ሖረ-ሄደ ካለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጉሙም የተላከ ሂያጅ፣ ልዑክ ማለት ነው፡፡ ወንጌለ መንግሥትን ድኅነተ ዓለምን ለመላው ዓለም ሊያውጁ ሊያበሥሩ ተልከዋልና፡፡ ቅዱስ ማርቆስ በወንጌሉ እንደገለጠው (ማር. 3.13) አስቀድሞ ከእርሱ ጋር እንዲኖሩ ከጠራቸው በኋላ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ የገለጠውን ድንቅ ሥራ አምላክ ሰው ሆኖ ያደረገውን ተአምራት ለዓለም ድኅነት የተደረገውን ሁሉ ሊመሠክሩ ተመርጠዋል፡፡

Monday, June 20, 2011

ምክንያተ ጡመራ ( My Reason For Blogging )


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በእግዚአብሔር አጋዥነት ጦማር ( ጽሕፈት ) እንጀምራለን
ረድኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ ካላደረጉ 
ልማር ላስተምር ፤ አነብ እተረጉም ፤ እጽፍ እደጉስ ቢሉ አይቻልምና

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማደግ በሰዎች የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ የሚከናወኑ ድርጊቶችን በመረጃ መረብ (Internet) አማካይነት ከአንዱ ክፍለ ዓለም ወደ ሌላው ክፍለ ዓለም ሀሳቦች ፣ አመለካከቶች እና አስተሳሰቦች ይንሸራሸራሉ፡፡
በሀገራችን በኢትዮጵያ ይህ ቴክኖሎጂ ከሌሎች ሀገሮች ጋር ሲነፃፀር በእጅጉ ያደገ ባይሆንም ቁጥሩ አነስተኛ የማይባል ተጠቃሚ በሀገር ውስጥ ይገኛል፡፡ በውጭው ዓለም ደግሞ በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን ተጠቃሚዎች መኖራቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው፡፡