Tuesday, January 29, 2013

36ቱ ቅዱሳት አንስት



36 ቅዱሳት አንስት ስም ዝርዝርና የመታሰቢያ ቀናቸው
36 ቅዱሳት አንስት አንዷማርያም መግደላዊት
ተቁ
ስም
የመታሰቢያ ቀናቸው
1
  ኤልሳቤጥ            
የካቲት 16 
2
  ሐና
መስከረም 7 ቀን
3
  ቤርዜዳን ወይም ቤርስት
ታህሳስ 10 ቀን
4
  መልቲዳን ወይም ማርና
ጥር 4 ቀን 
5
 ሰሎሜ
ግንቦት 25 ቀን    
6
 ማርያም መግደላዊት
ነሐሴ 6 ቀን
7
 ማርያም እንተ እፍረት እህተ አልአዛር
የካቲት 6 ቀን
8
 ሐና ነቢይት

Tuesday, January 15, 2013

ምሥጢረ ሥላሴ

                  እንኳን ለጥር ሥላሴ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ምሥጢር
አመሠጠረ ከሚለው ግስ የተገኘ ቃል ሲሆን ስውር ድብቅ ሽሽግ ማለት ሲሆን አምስቱ አዕማደ ምሥጢራትም ምሥጢር የተባሉበት ምክንያት
  • በሥጋዊ ጥበብ ምርምር መረዳት ስለማይቻሉ
  • ላመኑት እንጂ ላላመኑት ሰዎች የተሰወሩ በመሆኑ
 ምሥጢር በሁለት ይከፈላል፡፡ እነርሱም፡-
 የፈጣሪ ምሥጢር- ሊገለጥ የማይችል ነው፡፡ እስከ የሌለው ምሥጢርም ይባላል፡፡
 የፍጡራን ምሥጢር- በጊዜ የሚገለጥ /የሚታወቅ/ ነው፡፡ የሰውና የመላእክት ምሥጢር በዚህ ውስጥ የሚካተት ነው፡፡

Saturday, January 5, 2013

መጋቤ ሐዲስ ኃይለ ሚካኤል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፤ አሜን፡፡
ዋኅድ ዜና ሕይወት ወኅልፈት 
 ለክቡር  አባታችን   ኃይለ ሚካኤል
 ዘደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ ዓባይ
ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር፤ የጻድቅ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው፡፡/ መዝ 115፤6/
ቅድስት ይእቲ ኢየሩሳሌም ሀገረ ዳዊት መቅበርት፤
እስመ በውስቴታ ተሦአ ኃይለ ሚካኤል መሥዋዕት፡፡ ( በዕለቱ የቀረበ ጉባኤ ቃና ቅኔ)

መጋቤ ሐዲስ መምህር ኃይለ ሚካኤል ከኣባታቸው ከአቶ አስፋው ማሩ ( በስመ ክርስትናቸው ሣህለ ማርያም) እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ተዋበች ካሣ ( በስመ ክርስትናቸው ወለተ ኢየሱስ)  በድሮው ወሎ ጠቅላይ ግዛት በአሁኑ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት አማራ ሳይንት ውስጥ ምስካበ ቅዱሳን ገዳም ሕዳር 12 ቀን 1923 ዓ.ም. ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በዐራት ዐመታቸው ጀምረው በገዳሟ ከነበሩት መምህር ፋንታ ከፊደለ ሐዋርያ አንሥተው ዳዊት ደግመው ግብረ ዲቁናውን አጠናቅቀው በሰባት ዐመታቸው ከብጹዕ አቡነ ይስሐቅ ዲቁና ተቀበሉ፡፡ ከዚያ ጊዜ አንስተው ገዳሟን በዲቁና እያገለገሉ የቅስናውን ጓዝ ካጠኑ በኋላ በገዳሙ ከነበሩት መምህር ገብረ ጊዮርጊስ ቅኔ ተቀኙ፡፡