Saturday, August 20, 2011

ከመ ትንሳኤ ወልዳ ( እንደ ልጅዋ ትንሳኤ )


እንኳን አደረሳችሁ

ሰላም ለፍልሰተ ሥጋኪ ደባትረ ብርሃን ኀበ ተተክሉ
ለገነተ ጽባሕ በማዕከሉ
እመቤቴ ማርያም ሆይ በምስራቃዊ ተክለ ገነት መካከል የብርሃን ድንኳኖች ወደተተከሉበት 
ለዐረገ ሥጋሽ ሰላምታ ይገባል
መልክአ ማርያም
  ትንሣኤ በሁለት ይከፈላል ጊዜያዊና ዘለዓለማዊ በመባል ፡፡
ጊዜያዊ ትንሣኤ የሚባለው የእግዚአብሔር ከሃሊነት የሚገለጽበት ተኣምራዊ ሥራ ሆኖ በተወሰኑ ሰዎች ላይ ይፈጸምና ዳግም ሞትን የሚያስከትል ነው፡፡