Wednesday, May 30, 2012

ጰራቅሊጦስ


ቤተ ክርስቲያናችን ከምታከብራቸው ዓበይት በዓላት መካከል አንዱ በዓለ ጰራቅሊጦስ ነው፡፡ ይህ በዓል ጌታችን በሚያርግበት ጊዜ ደቀመዛሙርቱን አንትሙሰ ንበሩ ሀገረ ኢየሩሳሌም እሰከ ትለብሱ ኃይለ እም አርያም ሉቃ 2449 ብሏቸው አርጎ ነበር፡፡ተናግሮ የማያስቀር ነውና ባረገ በ10ኛው በተነሣ በ50ኛው ቀን ጰራቅሊጦስን ሰዶላቸዋል ፡፡



ጰራቅሊጦስ ማለት ፡-
1/ ናዛዚ(አጽናኝ) ማለት ነው ከመንፈስ ቅዱስ ሥራዎች አንዱ ያዘኑትን የተጨነቁትን በተለያየ ነገር ውስጥ ገብተው ግራ የተጋቡትን ሁለ ሰለሚያጽናና ናዛዚ ይባላል ፡፡
2/ከሣቲ (ምስጢር ገላጭ) ማለት ነው የተደበቀውን የሚገልጥ የረቀቀውን የሚያገዝፍ የተሰወረውን የሚያሳይ በመሆኑ ከሣቲ ( ምስጢር ገላጭ) ይባላል ፡፡

Wednesday, May 23, 2012

ዕርገት

 “ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን መዝ.465

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማታ ማታ እየወጣ የሚያድርባት፣ሐሙስ ሌሊት በይሁዳ በኩል ለአይሁድ ተላልፎ የተሰጠባት፣ሐዋርያት ስለ ነገረ ምጽአት ጠይቀው የተረዱባት፣ከሙታን ተለይቶ በተነሣ በአርባኛው ቀን ጌታችን ያረገባት ተራራ -ደብረ ዘይት።
ዐርገ የሚለው የግዕዝ ግስ ዐረገ፣ወጣ በሚሉት የአማርኛ ቃላት የሚፈታ ሲሆን ዕርገት የሚለው ስምም ማረግን፣ መውጣትን፣አወጣጥን ያመለክታል።(.. .)
ዕርገት ማለት መውጣት ወይንም ከፍ ከፍ ማለት ነው። ይኸውም ከአንድ ቦታ ወደ አንድ ቦታ መሄድን ይመለከታል። መጽሐፍ ቅዱስ የእግዚአብሔር ነቢይ የሆነው ኤልያስ ሳይሞት በሕይወት እያለ በእሳት ሰረገላ ላይ ተቀምጦ ወደ ሰማይ ማረጉን ይነግረናል። ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ማረጉን የአዲስ ኪዳን ጸሐፊዎች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።



Thursday, May 10, 2012

የቅዱሳን መሰወር (ኅብአተ ቅዱሳን) -ክፍል 2



ነቢዩ ኤልያስ
፬. ብሔረ ብፁዓን

ከኻያው ዓለማት ውስጥ የኾነች /ከመሬት ወገን የምትመደብ/ ስውር ምድር ብሔረ ብፁዓን ናት። እንደ ገድለ ዞሲማስ አገላለጽና ሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍት፥ በዚህች ቦታ ተሰውረው የሚኖሩ ሰዎች ራሳቸውን ለፈቃደ እግዚአብሔር ያስገዙ ናቸው። በውስጧም ቅዱስ ጋብቻን መፈጸም የሚችሉና ዘርን ለማሰቀረትና ለመተካት ልጅን መውለድ ይችላሉ። ለኃጥአን ያልተፈቀደች የማትገባም ቦታ ናት።

፭. ደብር ቅዱስ

ከምድር ወገን ሆና የተለየች ሥፍራ ናት። አዳም በበደለና ከገነት በወጣ ጊዜ ገነትን በማየት ይጸጸት ዘንድ በዚህች ሥፍራ አኑሮታል። መጽሐፍ ቅዱስ /ብሉይ ኪዳን/ ይህችን ቦታ «ደብር ቀዱስ፣ ከፍ የለች ሥፍራ» በማለት ይጠራታል። /ሄኖክ ፬፥፸፩/። አዳም ከአቤል ሞት በኋላ የተወለደለት ሴት ከነልጆቹ ይኖር እንደ ነበርና በኋላም በኖኅ ዘመን የቃየንን ሴቶች ልጆች በማየት ስተው መውረዳቸውን በዘፍጥረት ትርጓሜ እንረዳለን። «የእግዚአብሔር ልጆችም /በደብር ቅዱስ የሚኖሩ የሴት ልጆች/ የሰውን ሴት ልጆች /የቃየንን ልጆች/ መልካሞች እንደሆኑ አዩ፤ ከመረጧቸውም ሁሉ ሚስቶችን ለራሳቸው ወሰዱ።» /ዘፍ. ፮፥፪/ ይላል።

Friday, May 4, 2012

የቅዱሳን መሰወር (ኅብአተ ቅዱሳን) -ክፍል 1


ዮሐንስ ወንጌላዊ

የሰው ልጆች ወደ እግዚአብሔር በመንፈሳዊ አገልግሎት ባዘነበሉ መጠን ቸርነት የባሕርዩ የሆነ እግዚአብሔር ደግሞ የተለያየ መንፈሳዊ ብቃትን ይሰጣቸዋል፤ ሰማያዊ ምሥጢርን ይገልጥላቸዋል። ቅዱሳን በሥጋቸው በምድር ለጸሎት ቆመው ነፍሳቸው በተመስጦ ገነት መንግሥተ ሰማያት ተነጥቃ ሄዳ ከቅዱሳን መላእክት ጋር ታመሰግናለች። እንዲሁም በአካል እንደ ነቢያቱ ሄኖክና ኤልያስ በመወሰድ እስከ ጌታችን ዳግም ምጽአት መዳረሻ ቀን በመሰወር እንደሚኖሩ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዱናል።

«መሰወር» የሚለው ቃል የግእዝ ግሱ «ኀብአ»፦ «ሰወረ፥ መሰወር»፤ «ተኀብአ»፦ «ተደበቀ፥ ተሰወረ፥ ራቀ፥ ረቀቀ» ማለት ሲሆን በጥቅሉ ለዓይን እንዳይታይ እንዳይገኝ ሆነ፤ ለምሥጢርም ከሆነ ለአእምሮ ረቀቀ ማለት ነው ።

«መሰወርን» የምንዳስስበት ሃይማኖታዊ ጠገግ ወይም አድማስ በሥጋ ለባሽነት የኖሩትን የሰው ልጆችን በጽድቅና በቅድስና መሰወር የሚያካትት ነው። በዚህም መሠረት ከሰው ልጆች ወገን፦ በቅድስናቸው ብቃት፥ እግዚአብሔር በሰጣቸው ጸጋ እስከ ምጽአት ድረስ በሥጋቸው በብሔረ ሕያዋን እንዲሰወሩ፤ ከሰው ልጆች ዓይን ለጊዜው ለአስፈላጊ ሁኔታ እንዲሰወሩ፤ ከመደበኛ መልካቸው ለጊዜው ሌላ ሰው በመምሰል እንዲሰወሩ፤ መከራ እንዳያገኛቸው የሰወራቸውና ከሞቱ በኋላ ቅዱስ ሥጋቸውን የሰው ልጆች እንዳይቀብሯቸው የተሰወሩት ወዘተ ይገኙባቸዋል።