« እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦
የኀዘን የልቅሶና የጩኸት ድምጽ በራማ ተሰማ ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች ፤ የሉምና ስለ ልጆችዋ መጽናናትን እንቢ
አለች። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ድምጽሽን ከለቅሶ ዐይኖችሽንም ከእንባ ከልክየይ ፤ ለሥራሽ ፤ ዋጋ ይሆናልና ፥ ይላል፡፡
እግዚአብሔር ፤ ከጠላትም ምድር ይመለሳሉ። ለፍጻሜሽም ተስፋ አለ ፥ ይላል እግዚአብሔር ፥ ልጆችሽም ወደ ሀገራቸዎ ይመለሳሉ።
» ኤር ፴፮ ፥፲፭ ፡፡
![](https://blogger.googleusercontent.com/img/b/R29vZ2xl/AVvXsEg6MbKmZcAEkIlp0hUxhqc0xoPYk_JRTS6Wd5D766aHmLrJXWyu51hIM2ARNUkqRiTSregrShjMkq8YoYATd_MOz1hXWW7dk83SIvKUdYbYbxaJwTWGJJifcUJoq9TCB6xJ-LJn3ttV6Qc/s400/1-pic1.jpg) |
የቤተልሔም ህጻናት በግፍ
ሲገደሉ
|
ቅዱሳን ነቢያት
የሚናገሩት ስለ ዘመናቸው ብቻ አይደለም ፤ ከዘመናቸው ጋር በማገናዘብ ስላለፈው ይናገራሉ ፥ ስለሚመጣውም ይተነብያሉ። ዓረፍተ
ዘመን ሳይገታቸው ኃላፊያትንም መጻእያትንም ይተረጉማሉ። በመሆኑም ይህ ቃለ ኤርምያስ ወደኋላም ወደፊትም የሚሠራ ነው።
ለጊዜው እስራኤል ዘሥጋ በግብጽ የባርነት ዘመን የነበሩበትን ዘመን ያስታውሳል ፥ ለፍጻሜው ደግሞ በዘመነ ሥጋዌ መባቻ ማለትም
መድኅነ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ ጊዜ የተፈጸመውን ያሳያል።