Showing posts with label ሐዋርያት. Show all posts
Showing posts with label ሐዋርያት. Show all posts

Friday, July 11, 2014

ቅዱስ ጴጥሮስ

ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ ጳውሎስ

እንኳን ለቅዱስ ጴጥሮስ እና ለቅዱስ ጳውሎስ በዓለ ዕረፍት መታሰቢያ ሐምሌ 5 በሰላም አደረሳችሁ



በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ ሌላውም ያስታጥቅኻል ወደማትወደውም ይወስድሀል  
                  ዮሐ. 21÷18

ቅዱስ ጴጥሮስ




ቅዱስ ጴጥሮስ  የተወለደው በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው ቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ዮሐ. 1፥45፡፡ የአባቱ ስም ዮና ሲሆን ትውልዱም ከነገደ ሮቤል ነው፡፡ ዮና ከነገደ ስምዖን የምትሆን አንዲት ሴት አግብቶ ቅዱስ ጴጥሮስን ወለደ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም ከተወለደ በኋላ እንደ ሕገ ኦሪት ትእዛዝ በስምንተኛው ቀን ወደ ግዝረት ቤት አግብተው ስሙን በእናቱ ነገድ ስም ስምዖን ብለው ሰይመውታል፡፡
      እድሜው አምስት ዓመት ሲሆን እንደ አይሁድ ሥርዓት ሕገ ኦሪትን እየተማረ እንዲያድግ በቤተ ሳይዳ አጠግብ ወደሚገኘው ወደ ቅፍርናሆም ሰደዱት፡፡ በዘመኑ በባህር ዳር በምትገኘውና ታላቅ የንግድ መናኸርያ በነበረችው በፍቅር ናሆም የሮም ጭፍሮች አለቃ የነበረችው በቅፍርናሆም የሮም ጭፍሮች አለቃ የነበረው ኢያኢሮስ አይሁድን ደስ ለማሰኘት አሰርቶት በነበረው ምኩራብ እየተማረ አደገ፡፡
    

Tuesday, January 29, 2013

36ቱ ቅዱሳት አንስት



36 ቅዱሳት አንስት ስም ዝርዝርና የመታሰቢያ ቀናቸው
36 ቅዱሳት አንስት አንዷማርያም መግደላዊት
ተቁ
ስም
የመታሰቢያ ቀናቸው
1
  ኤልሳቤጥ            
የካቲት 16 
2
  ሐና
መስከረም 7 ቀን
3
  ቤርዜዳን ወይም ቤርስት
ታህሳስ 10 ቀን
4
  መልቲዳን ወይም ማርና
ጥር 4 ቀን 
5
 ሰሎሜ
ግንቦት 25 ቀን    
6
 ማርያም መግደላዊት
ነሐሴ 6 ቀን
7
 ማርያም እንተ እፍረት እህተ አልአዛር
የካቲት 6 ቀን
8
 ሐና ነቢይት

Sunday, July 17, 2011

የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያዊ ሥራ

የመጀመሪያው የቅዱስ ጳውሎስ ጉዞ

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪ (የሐዋ. 13.1-3) በአሕዛብ ሀገር ወንጌልን ለመስበክ ከበርናባስ ጋር ወጡ፡፡ በዚህ ጉዞቸው በጠቅላላ ወደ 2000 ኪ.ሜ የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል፡፡ ይህም ጉዞ የተከናወነው በ46 ዓ.ም አካባቢ ነው፡፡ የተሸፈኑትም ሀገሮች ሲሊንውቂያ፣ ቆጵሮስ፣ ስልማና፣ ጳፋ፣ ጰርጌን፣ ገላትያ፣ ጵስድያ፣ ኢቆንዮን፣ ሊቃኦንያ፣ ልስጥራ፣ ደርቤን፣ ጵንፍልያ፣ አታልያ እና አንጾኪያ ናቸው፡፡




Friday, July 15, 2011

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ


ትውልዱ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዘሩ ከዕብራውያን ከብንያም ነገድ ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው፡፡ድንኳን መስፋትን የተማረው በዚያ ነው። የሐዋ ፲፫፥፫ ጠርሴስ በንግድም የታወቀች የኪልቂያ ዋና ከተማ ናት፡፡ በከተማዋ እስከ አምስት መቶ ሺህ የሚገመት ከየሀገሩ የተሰባሰቡ ሕዝቦች ነበሩባት፡፡ ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነት ይሰጡ ስለነበር የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡ ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል፡፡ አባቱ የሮም ዜግነት ይኑረው እንጂ፡- ከብንያም ወገን የሆነ ፈሪሳዊ ነበረ። የሐዋ ፳፫፥፮። በፊልጵስዩስ መልእክቱ፡- «በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ ከእስራኤል ትውልድ፥ ከብንያም ወገን፥ ከዕብራውያን ዕብራዊ ነኝ፤ ስለ ሕግ ብትጠይቁኝ ፈሪሳዊ ነበርሁ፤ በሕግ ስለሚገኝ ጽድቅ ያለ ነቀፋ ነበርሁ።» ያለው ለዚህ ነው። ፊል ፫፥፭። ከታላቁ መምህር ከገማልያል እግር ስር ሆኖ ሕገ ኦሪትን እና የአይሁድን ወግ ጠንቅቆ ተምሯል። የሐዋ ፳፪፥፫።

Friday, June 24, 2011

ቅዱሳን ሐዋርያት ክፍል ፪

የሐዋርያት ዝርዝር
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሐዋርያት ዝርዝር በአራት ቦታዎች ተጽፎ ይገኛል፡፡ እነዚህ ዝርዝሮች በማቴዎስ፣ በማርቆስና በሉቃስ ወንጌሎች ሲገኙ በዮሐንስ ወንጌል ግን ዝርዝሩ አልሠፈረም፡፡ የመጨረሻው ዝርዝር የሚገኘው በሐዋርያት ሥራ ላይ ነው፡፡
ሐዋርያት  በበዓለ ሃምሳ