ሥርዐት ምንድን ነው?
“ወንድሞች ሆይ፡
ከእኛ እንደተቀበለው
ወግ ሳይሆን
ያለ ሥርዓት
ከሚሔድ ወንድም
ትለዩ ዘንድ
በጌታችን በኢየሱስ
ክርስቶስ ስም
እናዛችኋለን። …በእናንተ
ዘንድ ያለ
ሥርዐት አልሔድንምና።
“ (2ኛ ተሰ.
3፡ 6)
ሥርዐት የሥነ
ፍጥረት ሕይወት
ምሕዋር፣ መቆጣጠሪያ
መሣሪያ ነው።
የመዓልቱ በሌሊት፣
የሌሊቱ በመዓልቱ
በመሠልጠን ሥርዓተ
ዑደትን እንዳይጥስና
የመዓልቱ በመዓልቱ
የሌሊቱ በሌሊት
እየተመላለሰ ዕለታዊ
ግብሩን እንዲያከናውን
ማንኛውንም ፍጡር
ፈጣሪው በሥርዐት
አሰማርቶታል። (መዝ.
105፡19-24)
በተለይ መንፈሳዊያን ልዑካን መንፈሳዊውን ተልእኮ ያለ ሥርዓትና ያለ ሕግ ማካሔድ እንደማይችሉና እንደማይገባም ሐዋርያው አስተማረ። ያለ ሥርዐት ከሚካሔድ ወንድም ተለዩ” አለ። ስለሆነም በሰሙነ ሕማማት የሚከናወኑ ሃይማኖታዊ እሴቶች ከዚህ ኃይለ ትምህርት የተገኙ መሆናቸውን እያሰብን በሰሙነ ሕማማት የሚከናወኑ የሕማማት ሥርዐቶችን ቀጥለን እንመለከታለን።