Wednesday, February 8, 2012

አባ አርሳንዮስ


አባ አርሳንዮስ በ360 ዓ.ም በሮም ተወለደ፡፡ በዘመኑ ትምህርት በሚገባ የተማረና ለሴናተርነትም መዓርግ የደረሰ ሰው ነበር፡፡ የሮሙ ንጉሥ ቴዎዶስየስ ለልዕልት አርቃድዮስ እና ለልዕልት አኖሬዎስ መምህር አድርጎ መድቦት ነበር፡፡ በ394 ዓ.ም የሮምን ቤተ መንግሥት ንቆ ትቶ በድብቅ ወደ እስክንድርያ መጣ፡፡ በመቀጠልም ወደ ገዳመ አስቄጥስ ገብቶ የአባ ዮሐንስ ሐፂር ደቀ መዝሙር ሆነ፡፡ በገዳመ አስቄጥስ አጠገብ በሚገኘው በጴጥራ በምናኔ ይኖር ጀመር፡፡ የታወቁ ሦስት ደቀ መዛሙርት ነበሩት፡- እስክንድር፣ ዞይለስ እና ዳንኤል፡፡ ድሎት የለሽ ኑሮን በመኖር እና በአርምሞው የታወቀ አባት ነው፡፡ በ434 ዓ.ም ገዳመ አስቄጥስ ለሁለተኛ ጊዜ ከጠፋ በኋላ ወደ ትሮኤ ተራራ ወጣ፡፡ እዚያም በ449 ዓ.ም ዐረፈ፡፡

አባ አርሳንዮስ በቤተ መንግሥት በነበረበት ሰዓት ‹ጌታ ሆይ በድኅነት ጐዳና ምራኝ› እያለ ይጸልይ ነበር፡፡ እናም ‹አርሳንዮስ ›ሆይ ከሰዎች ተለይ ያን ጊዜ ድኅነትን ታገኛለህ› የሚል ድምጽ ሰማ፡፡ ወዲያውም ቤተ መንግሥቱን ትቶ ወደ ገዳም ገባ፡፡

Sunday, February 5, 2012

የኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ፈተና በሳዑዲ አረቢያ


35 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች የልደትን በዓል በማክበር ላይ እንዳሉ በቁጥጥር ሥር ውለው ተጠርፈው ወደሀገራቸው ሊላኩ ነው ፡፡
ቢቢሲ እንደዘገበው ( http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-16808429)

Some 35 Ethiopian Christians face deportation from Saudi Arabia for "illicit mingling", the global rights body Human Rights Watch (HRW) says.
Police arrested the group - including 29 women - after raiding a prayer meeting in the second city of Jeddah.
The women were subjected to strip searches and the men beaten and called "unbelievers", according to HRW.
In 2006, the Saudi government promised to stop interfering with private worship by non-Muslims.
The group was arrested in a private home as they gathered to pray during the run-up to Christmas, celebrated by Ethiopian Orthodox Christians on 7 January.

Saturday, February 4, 2012

የተባበሩት አረብ ኢሚሬት ሀገረ ስብከት

አቡዳቢ ፤ ዱባይ እና አላይን ፤ ቅኝት በፎቶ
ዘገባውን እመለስበታለሁ 












ክርስቲያን ወገኖቻችንን በሄዱበት መጽናኛ ይሆናቸው ዘንድ ቤተክርስቲያን መኖሩ ሁሉን ላዘጋጀ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይግባው ፡፡

የበረሃውን ዋዕይ ሳይሰቀቁ በማገልገል ላይ ላሉት

ብፁዕ አባታችን አቡነ ድሜጥሮስ
የሊባኖስ ፤ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ

መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ሰይፈ ገብርኤል የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ እና የአቡዳቢ ደብረሰላም መድኃዓኔለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ

መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ገሪማ የዱባይ ቻርጃ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ
መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ ወልደገብርኤል የአላይን ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ
እንዲሁም አገልጋይ ዲያቆናት እና ምዕመናን በሙሉ
ረጅም ዕድሜ እና ጤና ይስጥልን
አሜን
ከአቡዳቢ - የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ