Sunday, July 17, 2011

የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያዊ ሥራ

የመጀመሪያው የቅዱስ ጳውሎስ ጉዞ

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ ከተመለሰ በኋላ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪ (የሐዋ. 13.1-3) በአሕዛብ ሀገር ወንጌልን ለመስበክ ከበርናባስ ጋር ወጡ፡፡ በዚህ ጉዞቸው በጠቅላላ ወደ 2000 ኪ.ሜ የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል፡፡ ይህም ጉዞ የተከናወነው በ46 ዓ.ም አካባቢ ነው፡፡ የተሸፈኑትም ሀገሮች ሲሊንውቂያ፣ ቆጵሮስ፣ ስልማና፣ ጳፋ፣ ጰርጌን፣ ገላትያ፣ ጵስድያ፣ ኢቆንዮን፣ ሊቃኦንያ፣ ልስጥራ፣ ደርቤን፣ ጵንፍልያ፣ አታልያ እና አንጾኪያ ናቸው፡፡




Friday, July 15, 2011

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ


ትውልዱ
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዘሩ ከዕብራውያን ከብንያም ነገድ ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው፡፡ድንኳን መስፋትን የተማረው በዚያ ነው። የሐዋ ፲፫፥፫ ጠርሴስ በንግድም የታወቀች የኪልቂያ ዋና ከተማ ናት፡፡ በከተማዋ እስከ አምስት መቶ ሺህ የሚገመት ከየሀገሩ የተሰባሰቡ ሕዝቦች ነበሩባት፡፡ ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነት ይሰጡ ስለነበር የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡ ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል፡፡ አባቱ የሮም ዜግነት ይኑረው እንጂ፡- ከብንያም ወገን የሆነ ፈሪሳዊ ነበረ። የሐዋ ፳፫፥፮። በፊልጵስዩስ መልእክቱ፡- «በስምንተኛው ቀን የተገረዝሁ ከእስራኤል ትውልድ፥ ከብንያም ወገን፥ ከዕብራውያን ዕብራዊ ነኝ፤ ስለ ሕግ ብትጠይቁኝ ፈሪሳዊ ነበርሁ፤ በሕግ ስለሚገኝ ጽድቅ ያለ ነቀፋ ነበርሁ።» ያለው ለዚህ ነው። ፊል ፫፥፭። ከታላቁ መምህር ከገማልያል እግር ስር ሆኖ ሕገ ኦሪትን እና የአይሁድን ወግ ጠንቅቆ ተምሯል። የሐዋ ፳፪፥፫።

Thursday, July 7, 2011

አባ ሙሴ ጸሊም ኢትዮጵያዊ

አባ ሙሴ ጸሊም በትውልዱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን አስቀድሞ በውንብድና ኑሮ ሕይወቱን ይገፋ ነበር፡፡ ሰዎች ከገድሉ የተነሳ ያደንቁታል፡፡እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበርና እርሱ በሥጋው ጠንካራ ፤ በሥራውም ኃይለኛ ነበር፡፡
አባ ሙሴ ጸሊምም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ፤ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ፡፡ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር ፡፡

አባ ሙሴ ጸሊም  ኢትዮጵያዊ