Friday, April 18, 2025

 




✝️➕✝️➕✝️➕✝️➕✝️➕

 ዕለተ ዓርብ

✝️➕✝️➕✝️➕✝️➕✝️➕


➕ *ዓርብ ማለት መካተቻ መፈጸሚያ ማብቂያ ማለት ነው።* 


 *፩,* ✝️➕ እግዚአብሔር ፳፪ቱን ሥነፍጥረት ፈጥሮ የጨረሰበት ዕለት ነው። "እግዚአብሔርም የሠራውን ሥራ በሰባተኛው ቀን ፈጸመ፤ በሰባተኛውም ቀን ከሠራው ሥራ ሁሉ ዐረፈ።

እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም፤ እግዚአብሔር ሊያደርገው ከፈጠረው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአል"    ዘፍ ፪÷ ፪


 *፪* , ✝️➕አዳም አርባ ቀን የምድር ኑሮውን ጨርሶ ወደ ገነት የገባበት ዕለት  ነው ። "እግዚአብሔር አምላክም ሰውን ወስዶ ያበጃትም ይጠብቃትም ዘንድ በዔድን ገነት አኖረው" ዘፍ ፪ ÷ ፲፭


 *፫,* ✝️➕ አዳም የገነት ኑሮውን ፈጽሞ የተባረረበት ዕለት ነው። "ስለዚህ እግዚአብሔር አምላክ ከዔድን ገነት አስወጣው፥ የተገኘባትን መሬት ያርስ ዘንድ። አዳምንም አስወጣው፥ ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልባል ሰይፍን በዔድን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ"    ዘፍ ፫ ÷ ፳፫~፳፬


 *፬,* ✝️➕እስራኤል ፵ ዘመን መና ከደመና እየወረደላቸው ሲመገቡ ኑረው ርደተ መናው ተፈጽሞ የከነአንን ፍሬ መመገብ የጀመሩበት ዕለት ነው ። "ወዓርበ መና በፊንቆን እን 

እንጀራም በፊንቆን ቀረ የከነዓንንፍሬም መመገብ ጀመሩ" 


 *፭,* ✝️➕ *የክርስቶስ የሠላሳ ሦስት ዓመት ከሦስት ወር ጉዞ የነፍሳት አምሥት ሺኽ አምስት መቶ ዘመን ጉዞ ተፈጸመ "ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ “ተፈጸመ፡” አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ"* ዮሐ ፲፱÷፴


➡️ *ሲኦል ተነዋወጠች መሠረቶቿም እፈርስ እፈርስ አሉ* 

➡️ *ምድርን ያለጊዜዋ እንዳታልፍ አጸናት* 

➡️ *ደሙን በምድር ላይ አፈሰሰ ከኅልፈት ጠበቃት በእርሷ ያለውንም ሁሉ ጠበቀ* 

➡️ *ስለ ፍጥረት ሁሉ ሥጋውን በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ ተወው ነፍሱ ግን ወደ ሲኦል ወርዳ ከዚያው ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን አዳነች ሲኦልንም በዘበዘች ፍጥረትንም ሁሉ ገንዘብ አደረገች* 

➡️ *ሥጋውም በመቃብር ያሉ ሙታንን አስነሣ ነፍሱም በሲኦል የነበሩ ነፍሳትን ፈታች* 

           ሃይ አበ ዘአትና ፳፮ ÷ ፲፰~፳፩


 *፮,* ✝️➕ *በዕለተ ከእሑድ እስከ ዓርብ ተፈጥሮ በዕለተ ዓርብ ፍጻሜ ያገኘ ሥነ ፍጥረት በኅልፈት ፍጻሜ የሚያገኝ በዚህ እለት ነው ።* 

ወሶበ ተፈጸመ ኵሉ አሜሃ ለእሊአሁ ለኅሩያኒሁ ወለጻድቃኒሁ ደብተራ ብርሃን ይተክል ወመንጦላዕተ ብስሃን ይሰፍሕ ዘቦ ፯ቱ ምሥዋር 

ትርጕም፦ ሉሉ ከተፈጸመ በኋላ ያን ጊዜ ለመረጣቸው ለወዳጆቹ ለጻድቃኖቹ የብርሃን ድኖኳን ይተከላል ሰባት መሠወሪያ ያለው የብርሃን መጋረጃ ይዘረጋል 

       ቅዳሴ አትናቴዎስ  ፩÷ ፺፫


✝️➕✝️➕✝️➕✝️➕✝️➕

Saturday, April 5, 2025

ኒቆዲሞስ (የዐቢይ ጾም 7ኛ ሳምንት)




ጌታችን ወደዚህ ምድር መጥቶ የምስራቹን ቃል ሲያውጅ እስራኤላውያን የተቀበሉት በተደበላለቀ ስሜት ነበር፡፡ በአንድ በኩል ሕዝቡለብዙ ዘመናት በባርነት ሲገዛ ስለነበር ከሮማውያን ቅኝ ግዛት ነጻየሚያወጣቸው መሲህ ይፈልጋሉ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝቡ ለብዙ ዘመናትበባርነት ቀንበር ስለደከመ ተስፋ በመቁረጥ ተዳክሞ ነበር፡፡ መሲህ ቢመጣእንኳ ይመጣል ብለው የሚጠብቁት ጦር ይዞ ሰራዊት አስከትሎ ነው ብለውያምኑ ነበር፡፡ ስለዚህም ነው ክርስቶስን መሲህ ነኝ ብሎ ሲመጣ ለመቀበልፈቃደኞች አልነበሩም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ጦር ሳይዝ ሰራዊት ሳያስከትልእንዲሁ ባዶ እጁን አርነት ላወጣችሁ መጥቻለሁ እያለ ደጋግሞ ተናግሯልናነው፡፡ ምንም እንኳ አብዛኛው እስራኤላዊ የክርስቶስን መሲህነት ቢጠራጠርናባይቀበለውም፣ በፍጹም እምነት እስከ መጨረሻው  የተከተሉትም  ነበሩ፡፡ለዚህም  ትልቅ ማሳያ የሚሆነን ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ ኒቆዲሞስ የተባለአይሁዳዊ ነው፡፡ቅድስት ቤተክርስቲያንም ይህን  ታላቅ ሰው ለማዘከርየዐቢይን ጾም ሰባተኛ እሁድ በእርሱ ስም ሰይማ ታከብረዋለች ፡፡ ተከታዮቿምዕመናንም የእርሱን አሰረ ፍኖት እንዲከተሉ ትመክራለችታስተምራለችም፡፡  
ኒቆዲሞስ ማነው?
፩. ኒቆዲሞስ ፈሪሳዊ ነው  ዮሐ 3-1

Saturday, May 1, 2021

ትንሣኤ ዘክርስቶስ - የክርስቶስ ትንሳኤ



ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድኅነተ ዓለምን በመስቀል ላይ ከፈጸመ በኋላ በአካለ ሥጋ ወደ መቃብር ወረደ÷ ይኸውም በመቃብር ፈርሶ በስብሶ መቅረትን ሊያስቀርልን ነው፡፡ በአካለ ነፍስ ደግሞ ወደ ሲኦል ወረደ÷ ይኸውም በሲኦል ለነበሩ ነፍሳት ነፃነትን ይሰብክላቸው ዘንድ ነው፡፡ መለኮት፥ በተዋሕዶ፥ ከሥጋም ከነፍስም ጋር ነበረ፡፡ ለዚህ ነው፥ መቃብር ሥጋን ሊያስቀረው ያልቻለው፤ ሲኦልም ነፍስን ማስቀረት አልተቻለውም፡፡ ቅዱስ ዳዊት፡- « ነፍሴን በሲኦል አትተዋትምና ቅዱስህንም መበስበስን ያይ ዘንድ አትተዋትም» ያለው ይኽንን ታላቅ ምሥጢር በትንቢት ቃል ሲናገር ነው፡፡ መዝ ፲፭÷፲፡፡ ሐዋርያው  ቅዱስ ጴጥሮስም፡- «ክርስቶስ ደግሞ ወደ እግዚአብሔር (ወደ አብ÷ ወደ ራሱና ወደ መንፈስ ቅዱስ) እንዲያቀርበን፥ እርሱ ጻድቅ ሆኖ ስለ ዓመፀኞች አንድ ጊዜ በኃጢአት ምክንያት (ስለ ሰው ልጆች ኃጢአት ተላልፎ በመሰጠት) ሞቶአልና፤ በሥጋ ሞተ (በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ለየ)÷ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ÷ (ያን ሥጋ ነፍስ እንድተለየችው መለኰት አልተለየውም)÷ በእርሱም ደግሞ (መለኰት በተዋሐዳት ነፍስ) ሄዶ በወኅኒ ለነበሩት ነፍሳት ሰበከላቸው፤» ብሏል።